በአማራ ክልል ከታህሳስ 24 ቀን 2017 ዐ/ም ጀምሮ ዳግመኛ በተከሰተው የኮሌራ ወረርሽኝ 238 ሰዎች ሲያዙ የአራት ሰዎች ህይወት ማለፉ የክልሉ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ገልጷል።
በክልሉ የተከሰተው ወረርሽኝ በምዕራብ ጎንደር ዞን ቋራ ወረዳ ላይ ሲሆን በአሁኑ ጊዜ ወረርሽኙ በመስፋፋት በጎንደር ፣በባህርዳር፣በገንደውሀ ወረዳ እና በምዕራብ ጎጃም ቡሬ ከተማ ላይ መከሰቱን በኢንስቲትዩቱ የበሽታዎችና የጤና ሁኔታዎች ምላሽ አሰጣጥ ባለሙያ ሲስተር ሰፊ ደርብ ተናግረዋል ፡፡
የኮሌራ ወረርሽኙ በድጋሚ ታሕሳስ 24 ቀን 2017 ዓ.ም የተከሰተ መሆኑን ያነሱት ሲስተር ሰፊ ደርብ ከታሕሳስ 24 እስከ የካቲት 5 ባሉ ጊዜያት ብቻ 238 የሚሆኑ ዜጎች በወረርሽኝ መያዛቸውን አስታውቀዋል ፡፡
በተጨማሪም በወረርሽኙ ምክንያት የአራት ሰዎች ሕይወት ማለፉን ነግረውናል ፡፡
ወረርሽኙ እንዳይዛመት ህመምተኞች በተገኙበት የመኖሪያ አካባቢዎች ላይ ክሎሪን በመርጨት የብክለት መከላከል ስራዎች በክልሉ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በኩል እየተሰራ መሆኑ ተነስቶል ፡፡
የአደጋ ስጋት ተግባቦት የጤና ትምህርት በተከሰተባቸው እና በተስፋፋባቸው አካባቢዎች በመስጠት ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራ እየተሰራ መሆኑ ተነግሮል ፡፡
የካቲት 13 ቀን 2017 ዓ.ም
Related News
Golf
22 Feb, 2025
DOGE Put Him in the Treasury Department. . . .
Sports
13 Feb, 2025
Transfer: Onyedika debunks Club Brugge e . . .
Golf
21 Feb, 2025
Better United states of america Internet . . .
International
12 Feb, 2025
Meghan Markle issued awkward warning aft . . .
International
10 Feb, 2025
Coordinator to the PM for Climate Change . . .
Cricket
11 Feb, 2025
'Some Rules Also Apply': Zaheer Khan Cal . . .
International
21 Feb, 2025
New Delhi says it is looking into ‘deepl . . .
Sports
11 Feb, 2025
Carlo Ancelotti reveals who he expects t . . .