በአማራ ክልል ከታህሳስ 24 ቀን 2017 ዐ/ም ጀምሮ ዳግመኛ በተከሰተው የኮሌራ ወረርሽኝ 238 ሰዎች ሲያዙ የአራት ሰዎች ህይወት ማለፉ የክልሉ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ገልጷል።
በክልሉ የተከሰተው ወረርሽኝ በምዕራብ ጎንደር ዞን ቋራ ወረዳ ላይ ሲሆን በአሁኑ ጊዜ ወረርሽኙ በመስፋፋት በጎንደር ፣በባህርዳር፣በገንደውሀ ወረዳ እና በምዕራብ ጎጃም ቡሬ ከተማ ላይ መከሰቱን በኢንስቲትዩቱ የበሽታዎችና የጤና ሁኔታዎች ምላሽ አሰጣጥ ባለሙያ ሲስተር ሰፊ ደርብ ተናግረዋል ፡፡
የኮሌራ ወረርሽኙ በድጋሚ ታሕሳስ 24 ቀን 2017 ዓ.ም የተከሰተ መሆኑን ያነሱት ሲስተር ሰፊ ደርብ ከታሕሳስ 24 እስከ የካቲት 5 ባሉ ጊዜያት ብቻ 238 የሚሆኑ ዜጎች በወረርሽኝ መያዛቸውን አስታውቀዋል ፡፡
በተጨማሪም በወረርሽኙ ምክንያት የአራት ሰዎች ሕይወት ማለፉን ነግረውናል ፡፡
ወረርሽኙ እንዳይዛመት ህመምተኞች በተገኙበት የመኖሪያ አካባቢዎች ላይ ክሎሪን በመርጨት የብክለት መከላከል ስራዎች በክልሉ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በኩል እየተሰራ መሆኑ ተነስቶል ፡፡
የአደጋ ስጋት ተግባቦት የጤና ትምህርት በተከሰተባቸው እና በተስፋፋባቸው አካባቢዎች በመስጠት ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራ እየተሰራ መሆኑ ተነግሮል ፡፡
የካቲት 13 ቀን 2017 ዓ.ም
Related News
17 Apr, 2025
These 23 girls lacrosse teams are the bi . . .
08 Apr, 2025
Snooker traditionalists given hope as st . . .
02 Apr, 2025
Bruno Fernandes bust-up, comments on Man . . .
27 Mar, 2025
Flag football preview, 2025: Players to . . .
07 Apr, 2025
Raptors rookie Jonathan Mogbo has best g . . .
03 Apr, 2025
Sports News | Mourinho''s Quest for Titl . . .
23 Feb, 2025
Michael Hooper's return to rugby no fair . . .
07 Apr, 2025
Sports News | Narine Meets His 'fanboy' . . .