TRENDING NEWS
Back to news
21 Feb, 2025
Share:
በአማራ ክልል በተከሰተ የኮሌራ ወረርሽኝ 238 ሰዎች ሲያዙ  የአራት ሰዎች ህይወት ማለፉ ተገለፀ።
@Source: ethiofm107.com
በአማራ ክልል ከታህሳስ 24 ቀን 2017 ዐ/ም ጀምሮ ዳግመኛ በተከሰተው የኮሌራ ወረርሽኝ 238 ሰዎች ሲያዙ የአራት ሰዎች ህይወት ማለፉ የክልሉ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ገልጷል። በክልሉ የተከሰተው ወረርሽኝ በምዕራብ ጎንደር ዞን ቋራ ወረዳ ላይ ሲሆን በአሁኑ ጊዜ ወረርሽኙ በመስፋፋት በጎንደር ፣በባህርዳር፣በገንደውሀ ወረዳ እና በምዕራብ ጎጃም ቡሬ ከተማ ላይ መከሰቱን በኢንስቲትዩቱ የበሽታዎችና የጤና ሁኔታዎች ምላሽ አሰጣጥ ባለሙያ ሲስተር ሰፊ ደርብ ተናግረዋል ፡፡ የኮሌራ ወረርሽኙ በድጋሚ ታሕሳስ 24 ቀን 2017 ዓ.ም የተከሰተ መሆኑን ያነሱት ሲስተር ሰፊ ደርብ ከታሕሳስ 24 እስከ የካቲት 5 ባሉ ጊዜያት ብቻ 238 የሚሆኑ ዜጎች በወረርሽኝ መያዛቸውን አስታውቀዋል ፡፡ በተጨማሪም በወረርሽኙ ምክንያት የአራት ሰዎች ሕይወት ማለፉን ነግረውናል ፡፡ ወረርሽኙ እንዳይዛመት ህመምተኞች በተገኙበት የመኖሪያ አካባቢዎች ላይ ክሎሪን በመርጨት የብክለት መከላከል ስራዎች በክልሉ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በኩል እየተሰራ መሆኑ ተነስቶል ፡፡ የአደጋ ስጋት ተግባቦት የጤና ትምህርት በተከሰተባቸው እና በተስፋፋባቸው አካባቢዎች በመስጠት ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራ እየተሰራ መሆኑ ተነግሮል ፡፡ የካቲት 13 ቀን 2017 ዓ.ም
For advertisement: 510-931-9107
Copyright © 2025 Usfijitimes. All Rights Reserved.