በአማራ ክልል ከታህሳስ 24 ቀን 2017 ዐ/ም ጀምሮ ዳግመኛ በተከሰተው የኮሌራ ወረርሽኝ 238 ሰዎች ሲያዙ የአራት ሰዎች ህይወት ማለፉ የክልሉ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ገልጷል።
በክልሉ የተከሰተው ወረርሽኝ በምዕራብ ጎንደር ዞን ቋራ ወረዳ ላይ ሲሆን በአሁኑ ጊዜ ወረርሽኙ በመስፋፋት በጎንደር ፣በባህርዳር፣በገንደውሀ ወረዳ እና በምዕራብ ጎጃም ቡሬ ከተማ ላይ መከሰቱን በኢንስቲትዩቱ የበሽታዎችና የጤና ሁኔታዎች ምላሽ አሰጣጥ ባለሙያ ሲስተር ሰፊ ደርብ ተናግረዋል ፡፡
የኮሌራ ወረርሽኙ በድጋሚ ታሕሳስ 24 ቀን 2017 ዓ.ም የተከሰተ መሆኑን ያነሱት ሲስተር ሰፊ ደርብ ከታሕሳስ 24 እስከ የካቲት 5 ባሉ ጊዜያት ብቻ 238 የሚሆኑ ዜጎች በወረርሽኝ መያዛቸውን አስታውቀዋል ፡፡
በተጨማሪም በወረርሽኙ ምክንያት የአራት ሰዎች ሕይወት ማለፉን ነግረውናል ፡፡
ወረርሽኙ እንዳይዛመት ህመምተኞች በተገኙበት የመኖሪያ አካባቢዎች ላይ ክሎሪን በመርጨት የብክለት መከላከል ስራዎች በክልሉ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በኩል እየተሰራ መሆኑ ተነስቶል ፡፡
የአደጋ ስጋት ተግባቦት የጤና ትምህርት በተከሰተባቸው እና በተስፋፋባቸው አካባቢዎች በመስጠት ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራ እየተሰራ መሆኑ ተነግሮል ፡፡
የካቲት 13 ቀን 2017 ዓ.ም
Related News
11 Feb, 2025
'Some Rules Also Apply': Zaheer Khan Cal . . .
05 May, 2025
“Thank you Canon Curry” - Warriors fans . . .
27 Feb, 2025
Chinese fishing vessels used North Korea . . .
26 Apr, 2025
3 reasons why Chepauk hasn't been a for . . .
16 Apr, 2025
Dodger Stadium to host baseball, with su . . .
16 Apr, 2025
Breakthrough softball players: Players m . . .
10 May, 2025
2025 IIHF World Championship: Beniers, P . . .
07 May, 2025
Carrying a burner phone and 7 other prec . . .